የሚያዚያ 29፣2016 የዓለም ዜና
-መንገደኞችን አሳፍሮ ከሐዋሳ ወደ አዲስ አበባ ይበር የነበረ አንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ላይ እያለ የተፈጠረበት ጢስና መንጋጫገጭ መንገደኞችን ማስጋትና ማስጨነቁ ተነገረ።አዉሮፕላኑ አደጋ ሳይደርስበት አዲስ አበባ አርፏል።-የእስራኤል እግረኛ ጦር በሕዝብ የተጨናነቀችዉን የጋዛ የጠረፍ ከተማ ራፋሕን ለመዉረር መዘጋጀቱ አለም አቀፍ ሥጋትና ዉጥረት አስከትሏል።የፍልስጤም ራስ ገዝ መስተዳድር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የአዉሮጳ ሕብረት ራፋሕ እንዳትወረር አሜሪካ ጣልቃ ትገባ ዘንድ እየተማፀኑ ነዉ።-የሩሲያዉ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን መንግስታቸዉ ከምዕራባዉያን ባለንጦቹ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን አስታወቁ።