ዩኒቨርስቲዎች በፌደራል ፖሊስ እንዲጠበቁ መወሰኑ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 30 2012ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ያሉ ዩኒቨርስቲዎች ጥበቃ በፌደራል ፖሊስ እገዛ እና ክትትል እንዲካሄድ መወሰኑን የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር አስታወቀ።መስሪያ ቤቱ በተለይ ለDW በሰጠው መግለጫ በአንዳንድ ዩኒቨርስቲዎች የሚፈጠሩ ግጭቶች አካል ናቸው ከተባሉ የክልል ፖሊሶች አንዳንዶቹ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተናግሯል። የመቀሌ እና የሃዋሳ ዩኒቨርስቲዎች የመማር ማስተማር ሂደታቸው ሰላማዊ ቢሆንም በፌደራል ፖሊስ ጥበቃ ቢካሄድ የአካዳሚ ነጻነታቸውን እንደማይጋፋ አስታውቀዋል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ